|
|
|||
|
||||
Overview""የተራቡ የእግዚአብሔር ማዕደኞች"" የተባለው ይህ መጽሐፍ እ.ኤ.አ በ2026 የተጻፈና የታተመ ነው። ይህን መጽሐፍ የጻፍኩበት ዋና ምክንያት በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የደረሰብንን አደገኛ መንፈሳዊ ረሀብ ለማሳየት ነው። እንዲሁም ከሰማይ የሚመጣው የእግዚአብሔር ማዕድ ምን ማለት እንደሆነ፣ ማዕዱን የምንለይበት መንገድ፣ ማዕዱ በምድር ላይ የሚያከናውነው ተግባር ምን እንደሚመስል ከእግዚአብሔር የዘላለም አጀንዳ ጋር በማያያዝ በጥልቀት የተጻፈ ነው። በተጨማሪም አምስቱ የክርስቶስ ስጦታዎች በእግዚአብሔር ማዕድ ክርስቶስ በምድር ይሠራ በነበረበት የአላፊነት ክብደት ልክ ቀልድ የሌለውን ሥራ እንዲሠሩ የተጠሩ ናቸው። ታዲያ፦ ይህ ነው የማይባሉ በቊጥርም በዓይነትም ብዙ የተማሩ የነገረ መለኮት ምሁራን በየዘርፉ እያሉን ስለምን ተራብን? ስምን የተላበሱና የገነኑ ሐዋርያትና ነቢያት እያሉን እንዲት ልንራብ እንችላለን? ጥቅስን ከጥቅስ ጋር እያገናኙ የሚያስተምሩን ብዙ አስተማሪዎች በየስፍራው እያሉን ለምን በመንፈሳዊ ረሀብ ውስጥ ወደቅን? ለመንጎቻቸው የሰማዩን ምግብ እንዲመግቡ የተሾሙ እረኞች በየአጥቢያው እያሉን ለምን ጠኔ ያዘን? ለምን የእውነተኛው መንፈሳዊ ምግብ ጣዕም ጠፋብን? ሕዝቡን እናነቃቃለን በሚል አሳብ በብዙ ዋጋ አሉ የተባሉትን መዘምራንና የቃሉን አገልጋዮች በተደጋጋሚ ጋብዘን ለምን የሕዝቡ ረሀብ እየጨመረ መጣ? እኛም እንደ አይሁድ አለቆች በብዙ እውቀት የተሞሉ ""የአብያተ ክርስቲያን ኅብረት"" የሚባል ሸንጎ አለን፣ ጥያቄው፦ ይህ ሸንጎ ወይም ኅብረት እንደ ሐዋርያቱ ዘመን ሸንጎ ለሕዝቡ መንፈሳዊ ጥጋብን ያላመጣበት ምክንያት ምንድን ነው? የሚሉትን ጥያቄዎች የሚመልስ መጽሐፍ ነው። Full Product DetailsAuthor: Mekonnen MogesPublisher: Independently Published Imprint: Independently Published Dimensions: Width: 14.00cm , Height: 0.90cm , Length: 21.60cm Weight: 0.191kg ISBN: 9798250382434Pages: 160 Publication Date: 05 March 2026 Audience: General/trade , General Format: Paperback Publisher's Status: Active Availability: Available To Order We have confirmation that this item is in stock with the supplier. It will be ordered in for you and dispatched immediately. Language: Afrikaans Table of ContentsReviewsAuthor InformationTab Content 6Author Website:Countries AvailableAll regions |
||||