|
|
|||
|
||||
Overviewአሁን ባለንበት ዘመን ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ ለመድረስ ጂ.ፒ.ኤስ (GPS) እንጠቀማለን። ጂ.ፒ.ኤስ ሳተላይትን የሚጠቀም ቴክኖሎጂ ሲሆን፣ ከአንድ መልክዓ ምድር ወደ ሌላ መልክዓ ምድር ለመድረስ ተመራጭና አቋራጭ መንገዶችን እየመራ የሚያደርስ ነው። መንፈሳዊ ሕይወታችንም ወደ መዳረሻው ማምራት ያለበት የጉዞ እንቅስቃሴ ነው። የምንሄድበትን መዳረሻ ካላወቅን፣ ጂ.ፒ.ኤስ ልንጠቀም አንችልም። ጂ.ፒ.ኤስ ጥቅም የሚሰጠን መዳረሻችንን ካወቅን ነው። መዳረሻችንን ካላወቅን፣ ጂ.ፒ.ኤስ ሊመራን አይችልም። ስለዚህ፣ ጂ.ፒ.ኤስ ስንጠቀም ሦስት ቦታዎች አሉ፦ ያለንበት፣ የምናልፍበትና የምንደርስበት። ይህ መጽሐፍ በእነዚህ ሦስት ጽንሰ ሐሳቦች ላይ የተገነባ ነው፦ ያለንበት፣ የምናልፍበትና የምንደርስበት። መንፈሳዊ ሕይወታችን መዳረሻ (destiny) አለው። ነገር ግን ወደዚህ መዳረሻ መድረስ የምንችለው አሁን ያለንበትን ካወቅንና ወደ መዳረሻችን ለመድረስ መከተል ያለብንን መንገድ ስናውቅ ነው። ችግራችን መዳረሻችንን አለማወቅ ብቻ ሳይሆን፣ አሁን ያለንበትን በቅጡ ላንረዳው እንችላለን። እግዚአብሔር በቃሉ ውስጥ ያለንበትንም ሆነ የምንደርስበትን ያሳየናል። ያለንበትንና የምንደርስበትን ማሳየት ብቻ ሳይሆን፣ ካለንበት ተነሥተን ወደ መዳረሻችን የሚወስደንንም መንገድ ያሳየናል። ስለዚህ፣ መንፈሳዊ ጉዞአችን የተሳካ እንዲሆን ያለንበትን፣ የምናልፍበትንና የምንደርስበትን ማወቅ ይገባናል። Full Product DetailsAuthor: Ermias TilahunPublisher: Ermias Woldeyesus Imprint: Ermias Woldeyesus Dimensions: Width: 12.70cm , Height: 0.80cm , Length: 20.30cm Weight: 0.154kg ISBN: 9781087882093ISBN 10: 1087882095 Pages: 150 Publication Date: 07 October 2016 Audience: General/trade , General Format: Paperback Publisher's Status: Active Availability: Available To Order We have confirmation that this item is in stock with the supplier. It will be ordered in for you and dispatched immediately. Language: Amharic Table of ContentsReviewsAuthor InformationTab Content 6Author Website:Countries AvailableAll regions |
||||